የቨርጂኒያ የሕፃናት ጥበቃ ተጠያቂነት ስርዓት (ሲስተም) ከ 2009 ጀምሮ በአንድ ወይም በሌላ መልኩ በኮመንዌልዝ ውስጥ ለተዘገቡት የሕፃናት ጥቃት እና ቸልተኝነት ጉዳዮች ምላሽ መረጃ ሰብስቦ ለሕዝብ አቅርቧል። መረጃው የተገኘው ከሚከተሉት ኤጀንሲዎች ነው፡ Virginia Department of Social Services፣ የቨርጂኒያ ስቴት ፖሊስ፣ የቨርጂኒያ የወረዳ ፍርድ ቤቶች፣ የቨርጂኒያ የወጣቶች እና የቤት ውስጥ ግንኙነት ዲስትሪክት ፍርድ ቤቶች እና የቨርጂኒያ የወንጀል ፍርድ ኮሚሽን። የዚህ ድህረ ገጽ ሌሎች ገጾች ይህንን መረጃ ከ 2013 (የበጀት ዓመት ሐምሌ 1 - ሰኔ 30) እና ከዚያም በላይ ያሳያሉ፣ ይህ ገጽ ደግሞ ከ 2009 (የበጀት ዓመት) - 2012 (የበጀት ዓመት) የእነዚህን ሪፖርቶች ታሪካዊ ስሪቶች ያቀርባል። ይህንን ታሪካዊ መረጃ በአመት ከዚህ በታች ማውረድ እና ማየት ይችላሉ።